የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሽልማት የኢትዮጵያ ተሰሚነት ከፍ ማለቱን ያሳያል- አቶ ለማ መገርሳ
የመከላከያ ሚኒስትርና የኦሮሞ ዴሞክራክ ፓርቲ ም/ ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ ፓርቲያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸው ተከትሎ ስጦታ ባበረከተላቸው ወቅት እንደገለጹት፣ ሽልማቱ የኢትዮጵያ ተሰሚነት አንድ ደረጃ ከፍ የማለቱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያገኙት ሽልማት የሁሉም የአገሪቱ ህዝቦች ሽልማት ነው ብለዋል አቶ ለማ፡፡
አቶ ለማ መገርሳ ሌሎች ተመሳሳይ ሽልማቶችን ለማሸነፍ ጠንክረን መስራት አለብን ብለዋል፡፡
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ማዕከላዊ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በበኩላቸው፣ ሽልማቱ ሰላም ወዳድነታችን የዓለም አቀፍ እውቅና የማግኘቱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ሌሎችን መረጃ ለማግኘት የሚከተሉትን ፅሑፍ ይጫኑ
No comments:
Post a Comment