Thursday, October 17, 2019

በአፋር ክልል በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተደረጉ

በአፋር ክልል በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተደረጉ

በአፋር ክልል በአፋምቦ ወረዳ በኦብኖ ቀበሌ በሚኖሩ ንፁሃን አርብቶ አደር ሴቶች፣ ህፃናትና አዛውንቶች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ነው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሰላማዊ ሰልፍ የወጡት፡፡ በጥቃቱ በርካታ ዜጎች በታጠቁ ኃይሎች ተገለዋል፣ ሴቶች ተደፍረዋል፣ ንብረት ወድሙዋል። እነዚህ የታጠቁ ኃይሎች እነማን እንደሆኑና ከየት እንደመጡ እስካሁን መንግሥት የሰጠዉ መግለጫ የለም። ሆኖም ግን ጥቃቱ በተቀነባበረ ሙልኩ የተፈፀመ መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
በክልሉ ሰመራና አዋሽ ሰባት ኪሎን ጨምሮ ከሠሞኑ ሰልፍ ባልተካሄደባቸው የተለያዩ ከተሞች ሕዝቡ ዛሬ ጠዋት ወደ አደባባይ መውጣቱ ነው የተገለጸው፡፡
በከተሞቹ እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ ሰልፍ ዋና ዓላማው በንጹሃን ዜጎች ላይ በውስጥም ይሁን በውጭ ኃይሎች የሚደርሰውን ጥቃት ማውገዝና እንዲቆም መጠየቅ ነው ተብሏል፡፡
ሰልፈኞቹ መንግስት ጣልቃ በመግባት ዜጎቹን የመጠበቅና በእነርሱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የመከላከል ግዴታውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡







No comments:

Post a Comment

ከኢህአዴግ ምክር ቤት ፅ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

ከኢህአዴግ ምክር ቤት ፅ/ቤት የተሰጠ መግለጫ ኢህአዴግን ከግንባርነት ወደ አንድ ህብረ ብሄራዊ ውህድ ፓርቲ የማሸጋገር ጉዳይ በ1996 ዓ.ም ከተካሄደው 5ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ ጀምሮ በተከታታይ በተካሄዱት የድርጅቱ ጉባ...