በአፋር ክልል በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተደረጉ
በአፋር ክልል በአፋምቦ ወረዳ በኦብኖ ቀበሌ በሚኖሩ ንፁሃን አርብቶ አደር ሴቶች፣ ህፃናትና አዛውንቶች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ነው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሰላማዊ ሰልፍ የወጡት፡፡ በጥቃቱ በርካታ ዜጎች በታጠቁ ኃይሎች ተገለዋል፣ ሴቶች ተደፍረዋል፣ ንብረት ወድሙዋል። እነዚህ የታጠቁ ኃይሎች እነማን እንደሆኑና ከየት እንደመጡ እስካሁን መንግሥት የሰጠዉ መግለጫ የለም። ሆኖም ግን ጥቃቱ በተቀነባበረ ሙልኩ የተፈፀመ መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
No comments:
Post a Comment