የህወሓት መግለጫና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ምላሽ
የኢህአዴግ ጽሕፈት ቤትም ምላሽ ሰጥቷልየሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሰባት ቀናት ሲያካሄድ የነበረውን ስብሰባ በማጠናቀቅ መግለጫ አውጥቷል:: ህወሓት በመግለጫው “እሳትና ጭድ የሆኑ ፓርቲዎች ሊዋሃዱ አይችሉም ከተዋሃዱም ኢህአዴግ ከማፍረስ ባሻገር ሃገርን ያፈርሳል” ብልዋል::
የኢህአዴግ ፅሕፈት ቤት በበኩሉ “ውህደቱ ሃገራዊ አንድነት የሚፈጥር መሆኑን ያካሄድኩት ጥናት አሳይቷል” ብሏል::
በሌላ በኩል የጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሬስ ኃላፊ ወይም የፕሬስ ሴክሬታሪ ንጉሡ ጥላሁን በሰጡት ምላሽ፤ “በህወሓት የወጣው መግለጫ ለውጡ ከመጣላት ሳይሆን ከመጣበት ሕዝብን የማይወክል አካል የወጣ ነው” ብለዋል፡፡
ለዚህም ምክንያቱም “መግለጫውን ያወጣው ቡድን በለውጡ ምክንያት የተቋረጠበት ጥቅምና መኖሩንና የነበረው ግፍ እንዲመለስ መመኘቱ ነው” ብለዋል፡፡ ህወሓት የኢህ አዴግን የውህደት እንቅስቃሴ አስመልክቶ በመግለጫው ያሰፈረውም ለዓመታት ሲያንፀባርቀው ከነበረው አቋም የተለየ እንደሆነ አቶ ንጉሡ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሰን ሰፋ ያለ ዘገባ እናቀርባለን
No comments:
Post a Comment